Wednesday 27 January 2016

በወያኔው ፍርድ ቤት የቀረበው የሰማያዊ ፓርቲው ዮናታን ተስፋዬ ድጋሚ በቀጠሮ ወደ እስር ቤት ተመልሷል።



በወያኔው ፍርድ ቤት የቀረበው የሰማያዊ ፓርቲው ዮናታን ተስፋዬ ድጋሚ በቀጠሮ ወደ እስር ቤት ተመልሷል።
Negere Ethiopia's photo.
ፍ/ቤቱ ለ2ኛ ጊዜ 28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ሰጠ
*‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› ዮናታን ተስፋየ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኘው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለ2ኛ ጊዜ የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶበታል፡፡
ዛሬ ጥር 17/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበው አቶ ዮናታን ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀበትን ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለየካቲት 15/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ አቶ ዮናታን ተስፋየ የዋስትና መብቱ እንዲከበርለት ቢጠይቅም ፍርድ ቤቱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡
ፖሊስ በአቶ ዮናታን ላይ ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ሲጠይቅ ‹‹የቴክኒክ መረጃዎችን መሰብሰብ ይቀረናል፤ ያልተያዙ ግብረ አበሮችንም አሉ›› የሚል ምክንያት ማቅረቡን የተጠርጣሪ ጠበቃ ገልጸዋል፡፡
አቶ ዮናታን ተስፋየ በጠበቃ እና በቤተሰቦቹ እንዳይጎበኝ እንደተከለከለና ከታሰረበት ክፍል መታፈን የተነሳ የጤና እከል ቢገጥመውም ህክምና እንዳላገኘ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም አቤቱታውን አድምጦ በጠበቃውም ሆነ በቤተሰቦቹ እንዲጎበኝ እንዲፈቀድለትና ህክምናም እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ከጠበቃው ለማወቅ ተችሏል፡፡
አቶ ዮናታን ከችሎት ሲወጣ በስፍራው ለነበሩት ቤተሰቦቹና ወዳጆቹ ያለውን ፍቅር ገልጾ ‹‹ነጻነት ይሰማኛል›› በማለት ጮክ ብሎ ሲናገር ተደምጧል፡፡

በምዕራብ ወለጋዋ ጉደቱ አርጆ የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ “የሰው ሕይወት ጠፋ”


የአዲስ አበባንና የፊንፊኔ ዙሪያ ዞኖችን የከተሞች ማስፊፊያ እቅድ ተንተርሶከተቀሰቀሰውና በኦሮምያ ክልል የተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ትምሕርት ቤቶችተማሪዎች ሲያካሂዱ የቆዩት የተቃውሞ እንቅስቃሴ የክልሉ መንግስት እቅዱንመተዉን ካስታወቀም በኋላ በአንዳንድ አካባቢዎች አሁንም መቀጠሉ እየተዘገበ ነው።
ሰሞኑን በምዕራብ ወለጋ ጊዳ ወረዳ፤ ጉደቱ አርጆ ከተማ በተከናወነ የሰርግ ሥነ ሥርዓትላይ በጭፈራው መሃል የተቃውሞ ድምጽ ለማሰማት መካሄዱ የተነገረለትን እንቅስቃሴተከትሎ ተቃውሞውን ለማስቆም የመንግስት ኃይሎች በወሰዱት የኃይል እርምጃየአንድ ወጣት ሕይወት ማለፉንና ሌሎች ሦሥት ወጣቶች በጥይት ተመተውመቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ለአሜሪካ ድምጽ ገልጠዋል።

Sunday 24 January 2016

Ethiopian Demonstration in Sweden ,stockholm jun22/2016

Demonstration med etiopier i Stockholm igår fredag. Regimens väpnade styrkor har skjutit över 150 personer till döds den senaste månaden, i ett försök att stoppa massdemonstrationer och revolter

Friday 22 January 2016

European Parliament motion for resolution on the situation in Ethiopia

European Parliament, strongly condemns the recent use of excessive force by the security forces in Oromia and in all Ethiopian regions, the increased cases of human rights violations and abuses, including violations of people’s physical integrity, arbitrary arrests and illegal detentions, the use of torture, and violations of the freedom of the press and of expression, as well as the prevalence of impunity…
–   having regard its previous resolutions on the situation in EthiopiaEuropean Parliament
–   having regard to the statement by the EEAS spokesperson on recent clashes in Ethiopia, 23 December 2015
–   having regard to the joint statement by Federica Mogherini, High Representative for Foreign Affairs and Security Policy/Vice-President of the European Commission, and Minister of Foreign Affairs Tedros Adhanom of the Federal Republic of Ethiopia, 20 October 2015
–   having regard to the press release on the meeting between the High Representative/Vice-President Federica Mogherini and the Minister of Foreign Affairs of the Federal Republic of Ethiopia, Tedros Adhanom, 13 January 2016
–   having regard to the statement by the EEAS Spokesperson on elections in Ethiopia, 27 May 2015
–   having regard to the press release of the UN Office of the High Commissioner for Human Rights, 10 July 2015
–   having regard to press briefing note of the UN Office of the High Commissioner for Human Rights, 10 July 2015
–  having regard to the universal Declaration of Human Rights
–   having regard to the African Union Charter of Human and Peoples’ Rights
–   having regard to the UN the International Covenant on Civil and Political Rights,
–   having regard to Rule 123(2) its Rules of procedure
————————————–
A) whereas over the past two months , Ethiopia’s largest region, Oromia, has been hit by a wave of mass protests over the expansion of the municipal boundary of the capital, Addis Ababa which has posed risks for farmers eviction from their land;
B) whereas security forces used excessive lethal force and killed at least 140 protesters and injured many more, in what may be the biggest crisis to hit Ethiopia since the 2005 election violence;
C) whereas on the 14 January 2016 the government decided to cancel the disputed large scale urban development plan ; whereas if implemented, the plan will expand the city’s boundary by 20 times its current size; whereas Addis Ababa’s enlargement has already displaced millions of Oromo farmers and trapped them in poverty;
D) whereas the ethnic Oromos continue to suffer particular discrimination and human rights violations in efforts to suppress potential dissent in the region;
E) whereas the Ethiopian authorities arbitrarily arrested a number of peaceful protesters, journalists and opposition party leaders in the context of a brutal crackdown on the protests in the Oromia Region; whereas those arrested are at risk of torture and other ill-treatment;
F) whereas the government’s labelled largely peaceful protesters as ‘terrorists’ deploying military forces against them ;
G) whereas on December 23, the authorities arrested Bekele Gerba, deputy chairman of the Oromo Federalist Congress (OFC); Oromia’s largest legally registered political party; whereas Mr Gerba was being taken in a prison known for torture and other ill-treatment practices and shortly after he was reportedly hospitalized; whereas his whereabouts are now unknown, raising concerns of an enforced disappearance.
H) whereas other senior OFC leaders have been arbitrarily arrested in recent weeks or are said to be under virtual house arrest.
I) whereas last December leading activists such as Getachew Shiferaw (Editor-in-Chief: Negere Ethiopia), Yonathan Teressa (an online activist) and Fikadu Mirkana (Oromia Radio and TV) have been arrested arbitrarily though yet to be charged by the Ethiopian authorities.
J) whereas the current protests echo the bloody events of April and May 2014, when federal forces fired into groups of largely peaceful Oromo protesters, killing dozens; whereas at least hundreds more students were arrested, and many remain behind bars
K) whereas Ethiopia’s government has regularly been accusing people who express even mild criticism of government policy of association with terrorism; whereas dozens of journalists, bloggers, protesters, students and activists have been prosecuted under the country’s draconian 2009 Anti-Terrorism Proclamation.
L) whereas Ethiopia’s government imposes pervasive restrictions on independent civil society and media; whereas according to the Committee for the Protection of Journalist’s (CPJs) 2014 prison census found that Ethiopia was the fourth worst jailer of journalists in the world, with at least 17 journalists behind bars, whereas Ethiopia also ranked fourth on CPJ’s 2015 list of the 10 Most Censored Countries
M) whereas the Ethiopian authorities have routinely summoned to court the “Zone 9 bloggers” with terrorism charges for their writing over the past 2 years.
N) whereas numerous prisoners of conscience, imprisoned in previous years based solely on their peaceful exercise of their freedom of expression and opinion, including journalists and opposition political party members, remained in detention.; whereas these included some convicted in unfair trials, some whose trials continued, and some who continued to be detained without charge, among others Eskinder Nega, Temesghen Desalegn, Solomon Kebede, Yesuf Getachew, Woubshet Taye, Saleh Edris, and Tesfalidet Kidane
O) whereas severe restrictions on external funding continue to undermine the work and effectiveness of non-governmental organisations (NGOs) under the 2009 Charities and Societies Proclamation.
P) Whereas Ethiopia rejected recommendations to amend the Charities and Societies Proclamation and the Anti-Terrorism Proclamation that several countries made during the examination of its rights record under the Human Rights Council Universal Periodic Review in May 2014.
Q) Whereas Andargachew Tsige, a British-Ethiopian citizen and leader of an opposition party living in exile, was arrested in June 2014 while in transit through Yemen’s main airport and forcibly removed to Addis Ababa; whereas Tsige had been condemned to death several years earlier in his absence, and has been in death row practically incommunicado since then; whereas Juan Mendez, the UN special rapporteur on torture, has written to the Ethiopian and UK governments saying he is investigating the treatment of Tsige, following claims that Tsige is being deprived of sleep and held in isolation;
R) Whereas the Ethiopian government has de facto imposed a widespread blockade of the Ogaden region in Ethiopia, rich in oil and gas reserves; whereas attempts to work and report from the region by international media and humanitarian groups are seen as criminal acts, punishable under the anti-terrorist proclamation; whereas there are reports of war crimes and severe human rights violations perpetrated by the Army and government paramilitary forces against the Ogaden population;
S) whereas The Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), the ruling party coalition, won all 547 parliamentary seats in the May 2015 elections, due in part to the lack of space for critical or dissenting voices in the election process; whereas May’s federal elections took place in a general atmosphere of intimidation, and concerns over the lack of independence of the National Electoral Board;
T) Whereas Ethiopia enjoys political support from western donors and most of its regional neighbours, mostly due to its role as host of the African Union (AU) and its contribution to UN peacekeeping, security and aid partnerships with Western countries;
U) whereas Ethiopia receives more aid than any other African country – close to $3bn per year, or about half the national government budget
V.whereas for decades the government have been authorizing big development projects to foreign investors, which have been leading to severe land grabbing and millions vulnerable people often forcibly evicted and insensitively resettling; whereas often the government does not offer the local communities any alternative to permanent settlement and had not fully consulted groups before evicting them.
W) whereas some donors, including UK’s Department for International Development (DFID) and the World Bank, rechanneled funding from the problematic Protection of Basic Services (PBS) program in 2015 which was associated with the abusive “villagization program,” a government effort to relocate 1.5 million rural people into permanent villages, ostensibly to improve their access to basic services; whereas some of the relocations in the first year of the program in Gambella region in 2011 were accompanied by violence, including beatings and arbitrary arrests, and insufficient consultation and compensation
X) whereas Ethiopia is experiencing its worst drought in decades, deepening food insecurity and severe emaciation and unusual livestock deaths; whereas with 640 000 refugees, Ethiopia is the country in Africa with the highest number of refugees; whereas nearly 560 000 people are internally displaced due to floods , violent clashes over scarce resources and drought
Y) whereas the current political situation in Ethiopia and the brutal repression of dissent put a serious risk the security, development and stability in the country;
  1. Strongly condemns the recent use of excessive force by the security forces in Oromia and in all Ethiopian regions, the increased cases of human rights violations and abuses, including violations of people’s physical integrity, arbitrary arrests and illegal detentions, the use of torture, and violations of the freedom of the press and of expression, as well as the prevalence of impunity;
  2. Calls for an immediate end to violence, human rights violations and political intimidation and persecution;
  3. Urges for the immediate release of all those jailed for exercising their rights to peaceful assembly and freedom of expression, including students, farmers, opposition politicians, academics, bloggers and journalists ;
  4. Calls on the government to carry out a credible, transparent and impartial investigation into the killings of protesters and other alleged human rights violations in connection with the protest movement, and to fairly prosecute those responsible, regardless of rank or position;
  5. Welcomes the government’s decision to completely halt the Addis Ababa and Oromia special zone master plan, that plans to expand the municipal boundary of Addis Ababa. Calls for an immediate inclusive and transparent political dialogue, including the government, opposition parties, civil society representatives and the local population preventing any further violence or radicalisation of the population; takes the view that such dialogue, conducing to the democratisation of the country, is not possible under the current political conditions;
  6. Calls on the Government of Ethiopia to respect the Universal Declaration of Human Rights and the African Union Charter of Human and Peoples’ Rights, including the right to peaceful assembly, freedom of expression and association;
  7. Urges the government to immediately invite the UN Special Rapporteur on the rights to freedom of association and peaceful assembly and other UN human rights experts to visit Ethiopia to report on the situation;
  8. Calls on the government to stop suppressing the free flow of information, including by jamming media broadcasts and harassing media, including through intrusive surveillance programs, and facilitate access throughout Ethiopia for independent journalists and human rights monitors;
  9. Calls on the government to include local communities in a dialogue on the implementation of any large scale development project and ensure equal distribution of future benefits to the population ; to ensure that farmers and pastoralists are adequately compensated, preventing them from any arbitrary or forced displacement without consultation and adequate compensation.
  10. Expresses its concerns on the government’s forced resettlement program, known as “villagization program”.
  11. States that respect for human rights and the rule of law are crucial to the EU’s policies to promote development in Ethiopia and throughout the Horn of Africa;
  12. Call on the EU to effectively monitor programs and policies to ensure that EU development assistance is not contributing to human rights violations in Ethiopia, particularly programs linked to displacement of farmers and pastoralists, and develop strategies to minimize any negative impact of displacement within EU funded development projects;
  13. Further calls on the EU and Member States to react promptly to the escalation of violence and the deterioration of the human rights situation in the country by publicly and privately condemning the use of excessive force by security forces in Oromia and call on the government to exercise restraint in its response against protests and the exercise of basic freedoms by the Ethiopian people;
  14. Stresses that financial support to Ethiopia from the EU should be measured attending to the country’s human rights record and the degree to which the Ethiopian government promotes reforms towards democratisation, as the only way to ensure stability and sustainable development;
  15. Instructs its President to forward this resolution to the Government and the Parliament of Ethiopia, the European Commission, the Council, the Vice-President of the Commission/High Representative of the Union for Foreign Affairs and Security Policy, the institutions of the African Union and the Secretary-General of the United Nations.

Ethiopia’s Anti-Terrorism Law: A Tool to Stifle Dissent

Home » News » Ethiopia’s Anti-Terrorism Law: A Tool to Stifle Dissent

Ethiopia’s Anti-Terrorism Law: A Tool to Stifle Dissent

A Legal Analysis by International Lawyers
Oakland Institute & the Environmental Defender Law Center
Ethiopia’s Anti-Terrorism Law
Oakland, CA – With human rights as the special focus of the 26th Summit of the African Union that gets underway today in Ethiopia, the Oakland Institute and the Environmental Defender Law Center (EDLC) released a new report, Ethiopia’s Anti-Terrorism Law: A Tool to Stifle Dissent. This timely report, authored by lawyers from leading international law firms, provides an in-depth and damning analysis of Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation. Building on the substantial number of earlier legal analyses prepared by a wide range of critics of the law, the report examines how the law, enacted in 2009, is a tool of repression, designed and used by the Ethiopian Government to silence its critics.Ethiopia’s Anti-Terrorism Law
“While legitimate anti-terrorism laws exist, Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation criminalizes basic human rights, especially freedom of speech and assembly. The law defines terrorism in an extremely broad and vague way so as to give the government enormous leeway to punish words and acts that would be perfectly legal in a democracy,” said Lewis Gordon, editor of the report and Executive Director of the Environmental Defender Law Center. “It also gives the police and security services unprecedented new powers, and shifts the burden of proof to the accused. Worse still, many of those charged report having been tortured, and the so-called confessions that have been obtained as a result have been used against them at trial,” he continued.
“Through our extensive work on land related issues in Ethiopia, we have witnessed firsthand how the anti-terrorism law has been misused to curb peoples’ opposition to forced land evictions and land grabbing by domestic and foreign investors,” said Anuradha Mittal, Executive Director of The Oakland Institute. “We are grateful to the legal community for providing this essential analysis of the dire situation in Ethiopia. It is time for the international community and donor countries to demand that this law, used to oppress and intimidate political speech and freedom is struck down immediately,” Mittal continued.
“The conclusions reached in this report are not those of a few fringe lawyers or policy organizations,” said Lewis Gordon. “This law has been harshly criticized by the UN Commissioner for Human Rights, numerous UN Special Rapporteurs, the African Commission on Human and People’s Rights, the governments of the US and UK, and the EU. Given our findings, we must, as an international community, demand that until such time as Ethiopia revises this law to bring it into conformity with international standards, it repeal or suspend the use of this repressive piece of legislation.”
Those who have been charged as terrorists under the law include newspaper editors, indigenous leaders, land rights activists, bloggers, political opposition members, and students. Download/read the full report

***

About the report’s authors & contributor:

Lewis Gordon, Editor & Author: A Harvard graduate, Mr. Gordon has been a lawyer for over 35 years and is the Executive Director of the Environmental Defender Law Center (EDLC). Mr. Gordon has worked on numerous high-profile environmental and human rights cases on behalf of thousands of victims, as well as a host of international prize-winning activists, in dozens of countries around the world.
Sean Sullivan, Author: J.D., University of Southern California. Mr. Sullivan is a lawyer at the Los Angeles office of Davis Wright Tremaine, LLP, and focuses his practice on intellectual property and complex class action litigation. He has assisted EDLC on a number of projects in the past, including obtaining freedom for an international prize-winning Mexican activist wrongfully charged with murder, and obtaining political asylum for another imprisoned Mexican activist who had received an international prize delivered to him in his jail cell by the widow of the late Senator Robert F. Kennedy.
Sonal Mittal, Author: J.D. Harvard Law School. Ms. Mittal is an associate at the San Francisco office of Wilson Sonsini Goodrich & Rosati where she focuses her practice on privacy, data protection, and Internet law.
Kate Stone, Contributor. International Human Rights Law, University of Oxford. Kate Stone is a barrister specializing in international human rights law at Garden Court North Chambers, Manchester, UK.

UN experts urge Ethiopia to halt violent crackdown

UN experts urge Ethiopia to halt violent crackdown on Oromia protesters, ensure accountability for abuses

GENEVA (21 January 2016) – A group of United Nations human rights experts* today called on the Ethiopian authorities to end the ongoing crackdown on peaceful protests by the country’s security forces, who have reportedly killed more than 140 demonstrators and arrested scores more in the past nine weeks.united nations human rights
“The sheer number of people killed and arrested suggests that the Government of Ethiopia views the citizens as a hindrance, rather than a partner,” the independent experts said, while also expressing deep concern about allegations of enforced disappearances of several protesters.
The current wave of protests began in mid-November, in opposition to the Government’s ‘Addis Ababa Integrated Development Master Plan’ to expand the capital’s municipal boundary. The ‘Master Plan’ could reportedly lead to mass evictions and the seizure of agricultural land in the Oromia region, as well as extensive deforestation.
The UN experts welcomed the Government’s announcement on 12 January 2016 suspending the implementation of the ‘Master Plan’, but were concerned about continuous reports of killings, mass arrests, excessive use of force and other abuses by security forces.
“The Government’s decision is a positive development, but it cannot be seen as a sincere commitment until the security forces stop their crackdown on peaceful protests,” they said. “The role of security forces should be to protect demonstrators and to facilitate peaceful assemblies, not suppress them.”
“We call on the Government to immediately release protesters who seem to have been arrested for exercising their rights to freedom of peaceful assembly and expression, to reveal the whereabouts of those reportedly disappeared and to carry out an independent, transparent investigation into the security forces’ response to the protests,” the experts said.
“Accountability does not erase past abuses, but it is an important step towards rebuilding trust between people and their government,” they stressed. “Impunity, on the other hand, only perpetuates distrust, violence and more oppression.”
The UN independent experts also expressed grave concern over the Ethiopian Government’s application of the Anti-Terrorism Proclamation 652/2009 to arrest and prosecute protesters, labelling them as ‘terrorists’ without substantiated evidence. This law authorises the use of unrestrained force against suspects and pre-trial detention of up to four months.
“Ethiopia’s use of terrorism laws to criminalize peaceful dissent is a disturbing trend, not limited to the current wave of protests,” they experts noted. “The wanton labelling of peaceful activists as terrorists is not only a violation of international human rights law, it also contributes to an erosion of confidence in Ethiopia’s ability to fight real terrorism. This ultimately makes our world a more dangerous place.”
“There are bound to be policy disagreements in any society,” the human rights experts said, “but every Government has the responsibility to give space for people to peacefully express their views and to take these views into account.

European Parliament condemns Human Rights violations in Ethiopia


European Parliament strongly condemns the recent use of violence by the security forces and the increased number of cases of human rights violations in Ethiopia. It calls for a credible, transparent and independent investigation into the killings of at least 140 protesters and into other alleged human rights violations in connection with the protest movement after the May 2015 federal elections in the country.European Parliament
It also calls on the Ethiopian authorities to stop suppressing the free flow of information, to guarantee the rights of local civil society and media and to facilitate access throughout Ethiopia for independent journalists and human rights monitors. The EU, as the single largest donor, should ensure that EU development assistance is not contributing to human rights violations in Ethiopia,

Ethiopia: European Parliament debated on motion for resolution

Ethnic groups like the Oromo and the Amhara having a tough time because of their opposition work in Ethiopia…
European Parliament Plenary Session Debates on cases of breaches of human rights, democracy and the rule of law in Ethiopia.

Wednesday 13 January 2016

ሰብር ዜና የወያኔ ሰራዊት እርስ በእርሱ ተታኮሱ ከፍተኛም ጉዳት ደረሰ ተባለ

የመላዉ ኢትዮጵያ ህዝቦች ጠላት የሆነዉ እራሱን የትግራይ ነጻ አዉጭ ብሎ የሚጠራዉ የግፈኞች ስብስብ የሆነዉ ጎጠኛዉ ወያኔ በተለያዩ ከተሞች በዉትድርና ላይ ተሰማርተው የነበሩ የኦሮሞና የአማራ እንዲሁም የተለያየ ብሔር ያላቸዉን አባላት እና አርባ ምንጭ ላይ ከአሜሪካ ሰራዊት ጋር የነበረዉን መጠነኛ ብርጌድ በትግራይ ክልል ራማ ላይ በአንድነት አሰባስቦ! በካድሬዎቹ አማካኝነት፡
በኦሮሚያ ክልል ላይ የተነሳዉ ንቅናቄ የሚመራዉ በሽብርተኛ ሐይሎች በተለይም በኦነግና ! በርበኞች ግንቦት 7 ! ነዉ።
ዋነኛ አላማዉም ኢትዮጵያን አጥፍቶ ስልጣን በእጁ ማስገባት ብቻ ነዉ! 
ስለዚህም ይህን እንቅስቃሴ በማያዳግም እርምጃ መምታት አላማችን ነዉ!!
በሚል ዲስኩር ወር የዘለቀ ንትርክ እንደነበረ ምንጮች ሲገልጹ።
ከተለያዩ ክፍሎች የተዉጣጣዉ ሰራዊት በበኩሉ እኛ ከዚሁ ህዝብ ነዉ የወጣነዉ!
ለምን ወደዚህ ተነጥለንስ እንድንመጣ ተደረግን@!
ለምንስ ህዝባችን ላይ የማያዳግም እርምጃ እንድንወስድ ታግባቡናላችሁ!
በማለታቸዉ አለመግባባት የተፈጠረ ሲሆን በትናንትናው እለት በአንድ የአማራ ብሔር ተወላጅ ከፍተኛ መኮንን ትእዛዝ መሰረት 98 የሚደርሱ ልዩ ስልጡን ሐይሎች ከዚሁ ስብስብ ከሰራዊቱ በመነጠል እና ከራማ በመነሳት የወያኔን ወታደራዊ ቀለበት ቦርደር ጥበቃ ደምስሰዉ 23 ያህሉን በመግደል እና 13 በማቁሰል አስቸጋሪና ከባድ ዳገታማ ተራራ ወደ ሆነዉ አዲ በቕዩ በመገስገስ ላይ ሳሉ በድጋሚ ከተከታተላቸዉ የወያኔ ሐይል ጋር ተፋልመዉ ከ70 በላዩ በአዲቛላ ወደ ጎረቤት ሐገር በሰላም አልፈዉ መግባታቸዉ ከስፍራዉ እየተነገረ ነዉ።
ዛሬ በደረሰን መረጃ መሰረት ከወያኔ በኩል በአጠቃላይ 54 ቅጥረኞች መደመሰሳቸዉን ከስፍራዉ የደረሰን ምንጭ የወታደራዊ መረጃዉን ተነርተርሶ የገለጸ ሲሆን ድንበር ዘለል የእርስ በእርሱ ዉጊያ የፈጠረዉ ድባብ ዛሬም በራማ አካባቢ የሰፈረዉን ሰራዊት እንዳስደነበረዉ ለመረዳት ተችሏል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!
ጉድሽ ወያኔ
Gudish Weyane's photo.

በኦሮሚያ እና በሰሜን ጎንደር የተከሰተው የተቃውሞ እየተጋጋለ መሄድ እንጂ የመቀዛቀዝ ባህሪ አላሳየ – አፈንዲ ሙተቂ

oomiaamhara -satenaw
ሰሞኑን በኦሮሚያ እና በሰሜን ጎንደር የተከሰተው የተቃውሞ ንቅናቄ ሀገሪቱን ውጥረት ውስጥ ከትቷታል፡፡ አመጹ እየተጋጋለ መሄድ እንጂ የመቀዛቀዝ ባህሪ አላሳይ ብሏል፡፡ አሁንም በልዩ ልዩ አካባቢዎች ቀጥሏል፡፡ በአራቱም አቅጣጫዎች ውጥረት ሰፍኗል፡፡ በህይወት ዘመኔ ይህንን ያህል ዘላቂ ሆኖ የቆየ አመጽ አይቼ አላውቅም፡፡ በዚህ አመጽ ለጠፋው ህይወትና ንብረት እናዝናለን፡፡ በየትኛውም ወገን ሆኖ በትርኢቱ ውስጥ የተሳተፈው የኛው ዜጋ በመሆኑ ነፍሱና አካሉ ታሳዝነናለች፡፡
ታዲያ አመጹ የተከተሰው በመንግሥት ሚዲያ እንደሚነገረው “ኪራይ ሰብሳቢዎች፣ ግንቦት ሰባቶችና ኦነጎች በወጠኑት ሴራ ነው” የሚለው ምክንያት መሰረት የለውም፡፡ እንደዚህ ማለት “ህዝቡ አያገናዝብም፤ በማንም ይታለላል” የማለትን ያህል ነው፡፡ በኤርትራ የመሸጉት ድርጅቶችም ሆኑ “ኪራይ ሰብሳቢ” የሚባሉት የማይታወቁ ሃይሎች በዚህ አመጽ ላይ የተለየ ሚና የላቸውም፡፡ ድርጅቶቹ አመጹን ደግፈው መግለጫ መስጠታቸው የአመጹ ቀስቃሽም ሆነ መሪ ሃይል የሚያስብላቸው አይደለም፡፡
አመጹ የተወለደው የህዝብ ብሶቶች እንደ ኩሬ ውሃ እየተጠራቀሙ ከግድባቸው አልፈው መፍሰስ በመጀመራቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለነዚህ የህዝብ ብሶቶች ተጨባጭና ወቅታዊ ምላሽ እየሰጠ ኩሬውን ማድረቅ ነበረበት፡፡ ነገር ግን ከህዝብ ከሚነሳው ቅሬታ ይልቅ ካድሬዎቹ በሚጽፉት አማላይ ሪፖርት ስለሚታለል ስለብሶቶቹ የሚያወሳውን ሁሉ እንደ ተቃዋሚ ያይ ነበር፡፡ ትክክለኛ ተቃዋሚዎችን ደግሞ በአቋራጭ ስልጣን ለመያዝ የቋመጡ ተስፈኞችና ሁከት ፈጣሪዎች ብሎ ከመፈረጅ ውጪ እንደ ተቃዋሚ የማየት ችግር አለበት፡፡ ተቃዋሚዎች ከሚያነሱት የተቃውሞ ሃሳብ መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆነው በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሰረተ መሆኑን አይገነዘብም፡፡ የነዚህ ሁሉ ግድፈቶች ድምር ነው እንግዲህ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት እያሰለሱ ሲፈነዱ የነበሩትን አመጾች ሲቀሰቅሱ የነበሩት፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት አሁን አመጹን (በርሱ አገላለጽ “ሁከቱ”ን) ተቆጣጥሬአለሁ እያለ ነው፡፡ ነገር ግን ከሁኔታው ትምህርት ቀስሞ ለህዝብ ጥያቄዎች ተጨባጭ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ አሁንም ተመሳሳይ ስህተት ወደ መስራቱ ነው ያዘነበለው፡፡ ለምሳሌ በብዙ የኦሮሚያ እና የአማራ ክልል አካባቢዎች ሰዎች በገፍ እየታሰሩ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንትም ሁለት የኦፌኮ አመራር አባላት እና የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ታስረዋል (አንደኛው በቅርቡ የተለቀቁት አቶ በቀለ ገርባ ናቸው)፡፡ አንዳንድ ሰዎችም ከስራ ገበታቸው እየተወገዱ ስለመሆናቸውም እየተነገረ ነው፡፡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና መምህራንም ከትምህርታቸውና ከስራቸው መባረራቸውና መታሰራቸው ተዘግቧል፡፡ ይህ ሁሉ ባለፉት ሃያ አራት ዓመታት ሲደረግ ነበር፡፡ ነገር ግን ህዝቡ ይህንን ፈርቶ ለተቃውሞ እና ለአመጽ ከመውጣት አልታቀበም፡፡ ብሶቱ ሲያንገሸገሽው ለተቃውሞ ይወጣል፡፡ መንግሥት ለወደፊቱ ተመሳሳይ አመጽ እንዳይከሰት ከፈለገ የህዝቡን የልብ ትርታ ነው ማዳመጥ ያለበት፡፡ ዘወትር የሚወቀስበትን ተቃውሞን በጸጥታ ሃይል የመቆጣጠር ስልትን ተከትሎ በውጥረት ላይ ውጥረት መጨመር አይገባውም፡፡
—-
መንግሥት ራሱን አንቅቶ ሀገሪቱን መምራት የሚሻ ከሆነ በሶስት ደረጃዎች የሚተገበሩ እርምጃዎችን መውሰድ ያለበት ይመስለኛል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ከሚፈጸሙት ተግባራት መካከል የመጀመሪያው በቅርቡ የተካሄደው ንቅናቄ “የህዝብ አመጽ” መሆኑን ማመን እና ይህንኑ በየደረጃው ላሉት አባላትና ደጋፊዎቹ የማሳመን ስራ ነው፡፡ በምዕራብ ኦሮሚያ ጫፍ ከምትገኘው መንዲ ጀምሮ እስከ ምስራቅ ሀረርጌዋ የኮምቦልቻ ከተማ የሚኖረው ህዝብ የተሳተፈበትን ተቃውሞ “የጥቂት ነውጠኞች” ተቃውሞ እያሉ ማጥላላት አይቻልም፡፡
ንቅናቄው የኢህአዴግ መሪዎች በአድናቆት ከሚያወድሷቸው የራያ (ቀዳማይ ወያነ)፣ የጎጃም እና የባሌ ገበሬዎች አመጽ ጋር እንጂ አይተናነስም፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚለው ንቅናቄው የተለኮሰው “ሽብርተኞች፣ ኒዮ-ሊበራሎች፣ ጋኔሎች እና ጋንግስተሮች” ባደረጉት ቅስቀሳም አይደለም፡፡ ስለዚህ ተቃውሞው የህዝብ እንደሆነ ማመን ይገባል፡፡
ከመንግሥት የሚጠበቀው ሁለተኛው ተግባር ደግሞ ተቃውሞው የህገ-መንግሥት ይከበር ጥያቄ መሆኑን ማመንና ማሳመን ነው፡፡ ለምሳሌ በአዲስ አበባው ማስተር ፕላን ጉዳይ ላይ የቀረበው ጥያቄ የህገ-መንግሥት ይከበር ጥያቄ ነው፡፡ ህገ-መንግሥቱ “የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ላይ ልዩ መብት አለው” በማለት ደንግጎ ሳለ ከዚህ ድንጋጌ ጋር በቀጥታ የሚጋጭ ማስተር ፕላን መንደፍ ምን ማለት ነው…? አዲስ አበባ ለኦሮሚያ መስጠት የሚገባውን ልዩ ጥቅም ሳይሰጥ ሃያ ዘጠኝ የኦሮሚያ ከተሞችንና ከሚሊዮን የበለጠ ደሃ ገበሬ የሚኖርበትን መሬት ደረጃ በደረጃ በአዲስ አበባ ውስጥ ለማካለል መሞከር በየትኛው የህገ-መንግሥቱ አንቀጽ ነው የሚፈቀደው? በዚያ ላይ ማስተር ፕላኑ ከሁለት ዓመታት በፊት ደም ያፋሰሰ መሆኑ እየታወቀ እና ለወደፊቱ ይቀራል ተብሎ ለህዝቡ ተነግሮ ሳለ ዘንድሮ ላይ ለተፈጻሚነቱ መንቀሳቀስ ጥቅሙ ለማን ነው….?. ህዝቡ ከህግ አግባብ አልወጣም፡፡ የየማስተር ፕላኑን ጥያቄ ጨምሮ ህዝቡ የተንቀሳቀሰላቸው ሌሎች ታላላቅ ጥያቄዎች ሁሉ ህገ-መንግሥቱን የማስከበር ጥያቄ እንደሆነ ማመንና ለተፈጻሚነታቸው መንቀሳቀስ ተገቢ ይመስለኛል፡፡
ሶስተኛው ታላቅ ተግባር ደግሞ በመንግሥት የሚሰነዘሩ ሃሳቦችንም ሆነ ፖሊሲዎችን የማይቀበለውን ዜጋና ድርጅት እንደ ሀገር ጠላት አድርጎ የሚፈርጀውን ኮሚኒስታዊ እሳቤ ማቆም ነው፡፡ በተግባር እንደሚታወቀው ኮሚኒስቶች እነርሱን የሚቃወመውን ሁሉ እንደጠላት ነበር የሚፈርጁት፡፡ ይህ ኮሚኒስታዊ አረዳድ በሀገራችን ውስጥ ምን አይነት ጥፋት እንዳስከተለ እናውቃለን፡፡ ለቀይ ሽብር መከሰት ዋነኛው ምክንያት የነበረው በ1966 ዓብዮት ማግስት ባበቡት ድርጅቶች መካከል የነበረው የአቋም ልዩነት ሳይሆን ድርጅቶቹ ከነርሱ የተለየ ርዕዮት ያለውን ዜጋና ቡድን በጅምላ እንደ ጠላት የሚያዩበት ኮሚኒስታዊ (ግራ-ዘመም) ዘይቤአቸው ነው፡፡ ኢህአዴግም የኮሚኒዝም አቀንቃኝ በነበረበት ዘመን ከርሱ የሚለዩትን ሁሉ በጠላትነት ይፈርጅ ነበር፡፡ ታዲያ ዛሬ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ተከታይ ነኝ በሚልበት ዘመን እንኳ ከዚያ የጥንት ልማዱ ሙሉ በሙሉ አልተላቀቀም፡፡ ይህ ልማድ ካልቀረ ደግሞ ለሀገር በትክክል የሚያስበውን ዜጋ ለይቶ ማወቅ አይቻልም፡፡ ለሀገር ተቆርቁሮ በመንግሥት ፖሊሲዎችና የልማት ፕሮግራሞች ላይ ትችት የሚሰነዝረው በሙሉ እንደ ጠላት ስለሚፈረጅ የርሱ ሃሳብ አይደመጥም፡፡ የሚገርመው ደግሞ መንግሥት ብዙ ከተጓዘ በኋላ ከነዚህ ተቆርቋሪ ዜጎች የተሰነዘሩትን ሃሳቦች አምኖ የሚቀበል መሆኑ ነው፡፡ ምሳሌ ልስጣችሁ፡፡
በ1994/95 ሀገራችን ልክ እንደ አሁኑ በከፍተኛ ድርቅ ተመትታ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን የገበሬውን ህይወት ለመለወጥ በሚል መንግሥት በተግባር ላይ ካዋላቸው ፕሮግራሞች መካከል አንዱ “ውሃ ማቆር” የሚባለው ነው፡፡ ሃሳቡ በአጭሩ “ገበሬው በክረምትና በበልግ ወራት የሚዘንበውን ዝናብ በጉድጓድ አጠራቅሞ ዝናብ በጠፋበት ወቅት ይጠቀምበት” የሚል ነው፡፡ ይሁንና የተለያዩ የውሃ ኤክስፐርቶች ይህ አሰራር ሀገር አጥፊ መሆኑን ማስረጃ እየጠቀሱ ሞገቱ፡፡ ለምሳሌ “በኩሬ የተጠራቀመው ውሃ ቀስ በቀስ ወደ መሬት እየሰረጎደ ስለሚገባ የገበሬው ልፋት ከንቱ ሆኖ ይቀራል፤ በተጨማሪም በጉድጓዱ ውስጥ ደለል ስለሚገባበት ገበሬው የሚፈልገውን ያህል ውሃ ማጠራቀም አይቻልም” ተብሎ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ውሃው ለወባ መራቢያ አመቺ በመሆኑ በገበሬው ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል” የሚል ስጋት ከውሃ እና ከጤና ኤክስፐርቶች ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለነዚህ ሃሳቦች ዋጋ በመስጠት ፈንታ “ጠላቶቻችን ልማታችንን ለማደናቀፍ የሰነዘሩት ሃሳብ ነው” እያለ ማጥላላትን ነው የመረጠው፡፡
ይሁንና በሂደት ሁሉም ችግሮች ቀስ በቀስ እየታዩ መከሰት ጀመሩ፡፡ ውሃው ወደ ኩሬ ውስጥ ከገባ በኋላ በኩሬው ውስጥ ከመቆየት ይልቅ ወደ መሬት ውስጥ እየሰረጎደ እንደሚገባ ታወቀ፡፡ መንግሥት ይህንን ለማስቀረት በሚል በኩሬው ውስጥ ፕላስቲክ ይነጠፍ ማለት ጀመረ፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ግን ታላቅ አደጋ ተከሰተ! በዚያ የውሃ ማቆር ዘመቻ ሳቢያ ሀገሪቱ በታሪክ ያላየችው የወባ በሽታ ተጠቂ ሆነች!! መንግሥቱ በድርቅና በወባ ተወጠረ፡፡ አንደኛውን ችግር በአስቸኳይ ማስወገድ ስለነበረበት እንደዚያ የተለፋበትና የፕሮፓጋንዳ ጥሩምባ የተነፋለት የውሃ ማቆር ዘመቻ በ1997 አጋማሽ ላይ ለማንም ሳይነገር ተሰረዘ፡፡ ከዚያ በኋላ ስለርሱ ያወራ የለም፡፡ በቃ “የውሾን ነገር ያነሳ ውሾ” ሆኖ ቀረ!!!
የኢትዮጵያ መንግሥት ከያኔው ስህተቱ ተምሮ ከምሁራን የሚሰነዘሩ ሃሳቦችን መስማት ነበረበት፡፡ ነገር ግን አሁንም ከአስራ ሁለት ዓመታት በኋላ ጆሮውን ለምሁራን ውትወታ ሲከፍት አይታይም፡፡ በዚህ አያያዝ መቀጠል የህዝብ ብሶትን ማጠራቀም ነው የሚሆነው፡፡ ስለዚህ ሃሳብ የሰነዘረን ግለሰብ እና ቡድን አክብሮ ለሃሳቡ ዋጋ መስጠትና መመርመር፣ እንደዚሁም ሃሳቦቹን ጠቅልሎ ከመዘነ በኋላ ለተግባራዊነታቸው መንቀሳቀስ ይገባል፡፡
—–
በሁለተኛው ደረጃ ላይ የሚከናወኑት ተግባራት ከህዝቡ ህይወት ጋር በቀጥታ ለሚገናኙ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡባቸው ናቸው፡፡ ለምሳሌ ገበሬው ብሶት የሚያሰማበትን በግዴታ ላይ የተመሰረተ ማዳበሪያ የመጠቀም አሰራር እና ከተሜው ለሚማረርባቸው የኑሮ ውድነትና ስራ አጥነት አፋጣኝ መፍትሄዎችን መሻትን ይጨምራል፡፡ ሁሉም ዜጋ የሚንገሸገሽባቸው የመልካም አስተዳደር እጦትና የሙስና አሰራርም የመንግሥትን ፈጣን እርምጃ ይሻሉ፡፡ ከመደበኛ ነጋዴዎች የተለየ ድጋፍ የሚደረግላቸው ኢንዶውመንት ፈንድስ የሚባሉት ድርጅቶች (ኤፈርት፣ ጥረት፣ አምባሰል፣ ዲንሾ፣ ቱምሳ፣) ትክክለኛውን ህጋዊ መስመር ይዘው እንዲሰሩ መደረግ አለባቸው፡፡
ብዙዎች “የጆሮ ጠቢ ስርዓት” እያሉ የአንድ ለአምስት አደረጃጀትን ማስወገድና የወጣቶችና የሴቶች ሊግ አባላት ብቻ እየተመረጡ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የጥቃቅንና አነስተኛ ስራ ፈጠራ ፕሮጀክት ለብዙሃኑ ህዝብ ክፍት ማድረግ ይገባል ፡፡ በዚህ ረገድ የሚሰሙት ብሶቶች ከህዝቡ ህይወት ጋር በቀጥታ የተገናኙ በመሆናቸው ሌላ የህዝብ ቁጣ እንዲነሳ የማድረግ አቅማቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ብሶቶቹን በጊዜ ለመቅረፍ መንቀሳቀስ ይገባል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ የሚፈጸሙት ስትራቴጂያዊ እቅድ ወጥቶላቸው የሚተገበሩ ስራዎች ናቸው፡፡ ከነዚህም መካከል አንዱ አዲስ የከተሞች ልማት ስትራቴጂ መቅረጽ ነው፡፡ የኢህአዴግ መንግሥት እስከ አሁን ድረስ የሚሰራበት የከተሞች ልማት ስትራቴጂ አዲስ አበባን ወደ ጎን ከመለጠጥ እና አስከፊውን የመሬት ቅርምት ዘመቻ ከማባባስ ውጪ በከተሞቻችን እድገት ላይ ያመጣው ተጨባጭ ለውጥ አነስተኛ ነው፡፡ በአንዳንድ ከተሞች የተወሰኑ ፎቆችንና መለስተኛ ፋብሪካዎችን ለማየት ቢቻልም በከተሞቻችን መካከል ተመጣጣኝ እድገት ማምጣት አልተቻለውም፡፡ የመንግሥቱ ትኩረት በአዲስ አበባ ላይ ብቻ በመሆኑ የክልል ከተሞች ከእንፉቅቅ ጉዞ ሊወጡ አልቻሉም፡፡ አዲስ አበባ እየተለጠጠች በማስተር ፕላን ስም የኦሮሚያ መሬቶችን ለመዋጥ ያሰፈሰፈችው የፌዴራል መንግሥቱ ለከተማዋ የሰጠው ገደብ የለሽ አትኩሮት በርካታ ፍላጎቶችን ስለቀሰቀሰ ነው፡፡ ስለዚህ እንዲህ ዓይነቱ ወልጋዳ የከተሞች እድገት ስትራቴጂ ተወግዶ ሁሉም ከተሞቻችን ተጠቃሚ የሚሆኑበትን አዲስ የከተማ ልማት ስትራቴጂ መቀረጽ ይኖርበታል፡፡
ሌላው ደግሞ ዲሞክራሲን በትክክል የማስፈን ስራ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ቢታወጅም ሀገሪቱ በተጨባጭ የምትመራበት ስርዓት ስያሜ በየትኛውም መዝገበ-ቃላት ተፈልጎ የሚገኝ አይመስለኝም፡፡ ህገ መንግሥቱ ከአንዳንድ አንቀጾቹ በስተቀር በምዕራቡ ዓለም ያሉትን ህገ-መንግሥቶች ይመስላል (አብዛኛው ክፍሉ ከፈረንሳይ ህገ-መንግሥት የተገለበጠ ነው ይባላል)፡፡ በመሆኑም “ተራማጅ” ሊባል የሚችል ጤናማ ህገ-መንግሥት ነው፡፡ በአንዳንድ አንቀጾቹ ላይ (አንቀጽ 39፤ የመሬት አዋጅ ወዘተ…) የሚሰነዘሩት ጥያቄዎች ሀገሪቷ ወደ እውነተኛ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ኑሮ እድገት ውስጥ በምትገባበት ጊዜ በሚፈጠረው ብሄራዊ መግባባት ሊመለሱ ይችላሉ፡፡ ችግሩ ግን ኢህአዴግ እንዲህ ዓይነቱን ተራማጅ ህገ-መንግሥት አጽድቆ ለርሱ ተገቢውን አትኩሮት የማይሰጥ መሆኑ ነው፡፡ ድርጅቱ ከህገ-መንግሥቱ ይልቅ በፓርቲ ደረጃ ለሚመራባቸውና ለሚያምንባቸው መርሖዎች ከፍተኛ ስፍራ ይሰጣል፡፡ እነዚህ መርሖዎች በአብዛኛው ከቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የተገለበጡ ነው የሚመስሉት፡፡ እነዚህ የፓርቲው መርሖዎችና ህገ-መንግሥቱ ሰማይና መሬት ናቸው፡፡ ሁለቱ ባልተጣጣሙበት ሁኔታ ትክክለኛ ዲሞክራሲን ማስፈን አይቻልም፡፡ ስለዚህ ፓርቲው መርሖዎቹን እንደገና በህገ-መንግሥቱ አቅጣጫ አስተካክሎ ራሱን ለፉክክር ማዘጋጀትና ሀገሪቱ ከጭምብል ዲሞክራሲ ወደ እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የምትሸጋገርበትን ስርዓት ለመገንባት ሌት ከቀን መጣር አለበት፡፡
——
ከላይ በግሌ የሰነዘርኳቸው የመፍትሔ ሃሳቦች ሙሉእ አይደሉም፡፡ የህዝብን ብሶት ለማሻርና እምባውን ለማበስ የሚሰሩት ስራዎች በጣም በርካታ ናቸው፡፡ እኔ እነኝህን የመፍትሄ ሃሳቦች የጠቀስኳቸው ችግሮችን ዘርዝሬ መፍትሔዎችን ካልጠቆምኩ “ችግር ዘምዛሚ” የሚል ስም እንዳይሰጠኝ በመፍራቴ ብቻ ነው፡፡ ይሁንና መንግሥት መፍትሔ ሰጪ መሆንን የሚሻ ከሆነ እኔ የጻፍኩትን ባይሆን እንኳ ጉዳዩን ይበልጥ መዘርዘር ከሚችሉ ምሁራንና ተቋማት የሚሰነዘሩትን የምክር ሃሳቦች ይስማ እላለሁ፡፡ በልዩ ልዩ ከተሞች አመጹን ለማስቆም በሚል በጸጥታ ሃይሎች የሚካሄደው ግድያ፣ እስራትና ከስራ መፈናቀል በውጥረት ላይ ውጥረትን እየደራረበ ሀገሪቷን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ከመውሰድ ውጪ ወደ መፍትሔ አያመሩንም፡፡ ስለዚህ እነርሱን በአስቸኳይ ማቆምና ለህዝብ ጥያቄዎች መፍትሔ የመሻት ስራዎች ላይ መረባረብ ይገባል፡፡ “ህዝቡ መቶ ፐርሰንት መርጦኛል” የሚለው የኢትዮጵያ መንግሥት በእውነትም ለህዝብ ጥቅም የቆመ ህዝባዊ መንግሥት ከሆነ ጆሮውን ከፍቶ ህዝቡን ማዳመጥ አለበት፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ

ጸረ ሙስና ኮሚሽን በአባይ ጸሀዬ ሙስና ላይ መረጃ ቢደርሰውም ምርመራው እንዲቆም መታዘዙ ታወቀ

አቶ አባይ ጸሀዬ በዘመዶቻቸው ስም በርካታ መሬቶች መውስዳቸው፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ ባስቀመጡት ሃላፊ አማካይነት በመሬት ንግድ ከፍተኛ ጥቅም ማግኘታቸው፣ ህጋዊ ሰነድና ካርታ ያለው ቁልፍ ቦታ ከባለቤቱ ተነጥቆ ለእርሳቸው ዘመድ መሰጠቱ ሲረጋገጥ ምርመራው እንዲቆም መታዘዙ ታወቀ። በየክልሉ ተመሳሳይ ንቅዘት አለ።
በህዝብና በቦሌ ክፍለ ከተማ ሰራተኞች፣ እንዲሁም ለአብነት የተጠቀሱት ንብረታቸው የተወሰደባቸው ሴት ወ/ሮ ጉዳያቸውን የትኛውም ቦታ ሲወስዱ መጀመሪያ ቀጠሮ እንደሚሰጣቸው፣ በቀጠሮዋቸው ቀን ሲሄዱ ምን ምላሽ እንደማያገኙ ጠቅሰው ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት የተጀመረው የምርመራ ስራ ይህንን ይመስላል።
ቀደም ሲል ተጠሪነቱ ለአቶ መለስ የነበረው የፌደራል ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪዎች አቶ አባይ ጸሃዬን “የመሬት ከበርቴው” የሚል ስም ሰጥተዋቸዋል። ስያሜውም የተሰጣቸው በቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት ሲነግዱ ስለነበር ነው።
የኮሚሽኑ የጎልጉል ምንጭ እንዳመለከቱት አቶ አባይ ጸሀዬ መሬት ሲነግዱ እንደ ነበር የታወቀው በክፍለ ከተማው በተካሄደ ምርመራ ነው። በክፍለ ከተማው በጠራራ ጸሃይ የግለሰቦችን መሬት ሳይቀር እየቸበቸበ እንደሚገኝ ኮሚሽኑ በደረሰው ተደጋጋሚ ጥቆማ መሰረት የሚመለከተው መምሪያ መነሻ ጥናት ያዘጋጅና ምርመራው እንዲጀምር ይታዘዛል።
በዚሁ መሰረት የኮሚሽኑ መርማሪዎች ስራቸውን ይጀምራሉ። የኮሚሽኑ ባለሙያዎች ምርመራ እንደጀመሩ መሬት በህገወጥ መንገድ ሲቸበቸብ እንደነበር ይረዱና ከመሬት ጋር የተያያዙ መረጃዎችን ያሽጋሉ። የመሬት ልኬትም ሆነ ከመሬት ጋር የተያያዘ ስራ እንዳይሰራ ያግዳሉ። በተጨማሪም መሬት እየለኩ ሲሰጡ የነበሩ መሃንዲሶች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ ምርመራው በጥብቅ እንዲካሄድ ይደረጋል።
ክፍለ ከተማው ክልሉን ወደ ገጠር ቀበሌዎች እያሰፋ መሬት ይከልላል። መሬታቸው የተወሰደባቸው ደካማዎችን ቦሌ ክፍለ ከተማ ካሳ ለመውሰድ ሲንከራተቱ ማየት የተለመደ ነው። አራት ዓመት፣ አምስት ዓመት ከዚያም በላይ ካሳ ሳያገኙ የሚመላለሱ ደካሞች አሁን ድረስ አሉ። ባለንብረት ለንብረቱ ካሳ የሚከፍለው አጥቶ ይንከራተታል፤ መሬት የመንግስት እንደሆነ ያወጀው መንግስት በከፍተኛ ባለስልጣኖቹ አማካይነት መሬት አየር በአየር ይቸበችባል። ይህ የአሰራሩ ግድፈት ሲሆን ለአብነት የተጠቆመው ጉዳይ አስከፊነትና የወንጀሉ ርህራሄ አልባነት እዚህ ላይ ጎልቶ ይታያል።
አሳዛኝ የተባለው የምርመራ ውጤት ታሪክ የሚጀምርው እዚህ ላይ ነው። መሃንዲሶች በሙሉ ታስረው ተመረመሩ። ምርመራው በሙሉ ወደ አንድ ሰው ቢያመላክትም ያንን ሰው ደፍሮ የሚናገር ጠፋ። ይህን ጊዜ “ለምን” የሚል ጥያቄ ተነሳ። የመሬት አስተዳደር ሃላፊውና የክፍለከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጉዳዩ የማይመለከታቸው ተደርጎ መወሰዱ፤ መሬት በህገወጥ ስለመቸብቸቡ በቂ መረጃና ማስረጃ በቀረበበት ሁኔታ፣ መሬታቸውን በግፍ ተነጥቀው ለሌላ ሰው የተሰጠባቸው እንዳሉ ተረጋግጦ ሳለ ካርታ ላይ የሚፈርሙትና ለመሃንዲሶች ትዕዛዝ የሚያስተላልፉት የመሬት አስተዳደር እንዲታሰሩና እንዲመረመሩ አለመደረጉ በጓሮ ኮሚሽኑ የሚታማበት ጉዳይ ሆነ። “ጥርስ የሌለው አንበሳና የመለስ አሽከር” የሚለው የኮሚሽኑ ስም በስፋት ተነሳ!!
“ለፀረሙስና ኮሚሽን ሌላ ጸረ ሙስና ኮሚሽን” በሚል የክፍለ ከተማው ሰራተኛ የሆኑ ደብዳቤ በመጻፍ ወቀሳ ሰንዝረው ምርመራው በወጉ እንዲከናወን ጥቆማና አስተያየታቸውን ላኩ። አንዳንድ ስማቸውንና ማንነታቸውን የደበቁ ሰዎች ጉዳዩን ለግል ሚዲያና ለመንግስት መገናኛዎች እንደሚያቀብሉ ዛቱ። ማንም ምን ቢል የሚሰማም የሚደነግጥም ጠፋ።
ምርመራ ከተደረገባቸው ጉዳዮች መካከል ለአብነት የተቀመጠው ዛሬ ህንጻ በብድር ተገነብቶበት ከፍተኛ ኪራይ የሚሰበሰብበት ከመገናኛ ወደ ገርጂ በሚወስደው አዲሱ ጎዳና ዳር ላይ ያለ አንድ ቦታ ጉዳይ ሲጎተት ሚስጥሩን ገለጠው። የመረጃው ምንጭ እንዳስረዱት ምርመራውን የያዘው ባልደረባቸው እንደነገራቸው ምስጢሩ ሲገለጽ ማመን አቅቶት ነበር።
ለክፍለከተማው የመሬት አስተዳደር ሃላፊ ቅርብ ተጠሪ የሆነው መሃንዲስ ምርመራ ሲካሄድበት “እንግዲያውስ እውነቱ ይህ ነው” በማለት አብራራ። በግፍ የተወሰደው ከላይ የተገለጸው ቦታ የተሰጠው ለአቶ አባይ ጸሃዬ ዘመድ መሆኑን ይፋ አደረገ። መሬቱ የቀድሞው ባለቤቶች ለመሆኑ የሚገልጽ በቂ ማስረጃ እንዳለው ቢታወቅም አለቃው አዲስ የባለቤትነት ማስረጃ ቀደም ሲል እንደነበር ተደርጎ እንዲያዘጋጅ ባዘዘው መሰረት የሰው ንብረት አሳልፎ መስጠቱን አስታወቀ። ይህን ጊዜ ምርመራው ባስቸኳይ ወደ ሌላ መርማሪ እንዲዛወር ተደረገ።
የቦሌ ክፍለ ከተማ የመሬት አስተዳደር ሃላፊ አቶ መሠረት የአቶ አባይ ጸሃዬ የቅርብ የስጋ ዘመድ ሲሆኑ፣ በእርሳቸው ትዕዛዝና አጽዳቂነት በክፍለ ከተማው በርካታ ቁልፍ ቦታዎች ለዘመድ አዝማድ በሽርክና፣ ለባለ ገንዘብ በሽያጭ እንዲዘዋወሩ መደረጉ በምርመራ እንደታወቀ አስቸኳይ መመሪያ ተላለፈ።
መመሪያው እስረኛው መሃንዲስ ባስቸኳይ እንዲለቀቅ፣ ምርመራውም እንዲቋረጥ የሚል ነበር። ከፍተኛ የሙስና ወንጀልና የስነምግበር ጉድለት መከሰቱን፣ በግፍ ንብረታቸውን ተቀምተው ባዶ እጃቸውን የቀሩ እንዳሉና፣ በማስፋፊያ ስም ቁልፍ ቦታዎች ከህግ ውጪ መተላለፋቸውን ይፋ ለማድረግ ሰፊ ጊዜ ወስዶ የተሰራው ስራ ሙሉ በሙሉ ይፋ ሳይሆን ተዳፈነ። የተልከሰከሰ የስራ ሪፖርት እንዲቀርብ ተደርጎ ፋይሉ ተዘጋ። ከእስር የተፈታው መሃንዲስም ደብዛ ጠፋ። የአገር ደህንነት ከበርካታ ተመሳሳይ ወንጀሎች ጋር ጉዳዩን እንደያዘው የጎልጉል ዘጋቢ አረጋግጧል።
የድርጊቱ ዋና ተዋናይ የአቶ አባይ ዘመድ እንኳንስ ሊታሰሩ በእድገት የከንቲባ ኩማ ደመቅሳ አማካሪ ሆነው አዲስ አበባ አስተዳደር ተመደቡ። ዋና ስራ አሰፈጻሚው የፌደራል ስራና ከተማ ልማት ሚኒስትር ውስጥ ከፍተኛ ሹመት ተሰጣቸው። በአሁኑ ወቅት የከንቲባው አማካሪ የሆኑት የአባይ ጸሃዬ ዘመድ መሬትን አስመልክተው ኪራይ ሰብሳቢነት ስለመስፋፋቱ ክፍለ ከተሞችን ሰብስበው ይሰብካሉ። ስለ ሙስና አደገኛነት በየመድረኩ እንዲያስተምሩ ተደረገ። ድርጊቱ በርካቶችን አስቆጣ። በርካታ የወቀሳ ደብዳቤ ለኮሚሽኑ ጎረፈለት። በአካል ቀርበው ምስክርነት የሰጡና ኮሚሽኑ ሊመሰርት አቅዶት ለነበረው ክስ ምስክር ለመሆን የተስማሙ ደነገጡ።
ጉዳዩ እንዲዳፈን ስለተደረገበት ምክንያት ሲያስረዱ “በየትኛውም ደረጃ ያሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ በደህንነት ውስጥ ያሉ ባለስልጣናትና መካከለኛ ደረጃ ሃላፊዎች በግልጽ ሙስና ውስጥ መዘፈቃቸው በመረጃ ቢቀርብም ኮሚሽኑ እርምጃ የማይወስደው ሙስና አንዱ የስርዓቱ እድሜ ማራዘሚያ መንገድ በመሆኑ ነው” ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል።
“ኢህአዴግን እያገለገሉ ያሉ ባለስልጣኖች ህወሃትን በሚገባ መከራከር የማይችሉትና በታዛዥነት እያጎበደዱ ለመኖር የሚገደዱት የገቡበትን የሙስና ማጥ ስለሚያውቁት ከተቃወምን እንታሰራለን” በሚል ፍርሃቻ መሆኑን የኮሚሽኑ ባልደረባ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ምንጭ ተናግረዋል። ባለሙያው አያይዘውም “በአገሪቱ የተንሰራፋው ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል፤ ከላይ እስከታች ተበለሻሽቷል” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
“ባለሥልጣናትን በሙስና ማበስበስ” የስርዓቱ ዋንኛ የማኮሰሻና የማዋረጃ ስልት እንደሆነ የተለያዩ ማስረጃዎችን በማጣቀስ “አቶ መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ” በሚል ርዕስ ባቀረብነው ቃለ ምልልስ ማስነበባችን ይታወሳል። ኢህአዴግ ለትምህርት ውጪ አገር የላከቸውና ስማቸውን ለጊዜው መግለጽ ያልፈለጉት ተናጋሪ “ስርዓቱ በስብሷል” ባይ ናቸው።
“ባለኝ መረጃ መሰረት የኔ ስጋት እነዚህ ያለቀረጥ የሚነግዱ፣ ገንዘብ የሚያቀባብሉ፣ የገንዘብ ዝውውር ላይ የተሰማሩ፣ ድርጅት ያላቸው፣ በቅጽበት ተመንጥቀው ባለሚሊዮኖች የሆኑ፣ የባንክ ብቸኛ ተጠቃሚዎች፣ ሸቃጮችና አወራራጆች ከትንሽ እስከ ትልቅ ስራውን የሚሰሩት ከባለስልጣናት ጋር ነው። ከመከላከያ አመራሮች ጋር ነው። ከደህንነትና ከዋናው የስልጣን እርከን ጋር በመመሳጠርም ነው” በማለት ቃለ ምልልስ አድራጊው በውል የሚያውቁትን ተናግረዋል። አያይዘውም “ስርዓት ሲበሰብስ ልዩ ምልክቱ ትናንሽ መንግስታት ማቆጥቆጣቸው ነው። በኢህአዴግ መበስበስ አቶ መለስን ጨምሮ በርካቶች ይስማማሉ። ኢህአዴግ መዓዛውን አልቀየረም የሚሉት በአገሪቱ ድፍን ቆዳ ላይ የራሳቸውን መንግስት የተከሉ ተጠቃሚዎች ብቻ ናቸው። እነሱ ክሬሙን እየላሱ ስለሆነ የመበስበስ አደጋ አይታያቸውም። ስለመበስበስ ለማሰብም ጊዜ የላቸውም። የበሰበሰው ነገር ሲናድ የሚበላው ግን አስቀድሞ እነሱን ነው። ምክንያቱም አቶ መለስ የቆፈሩት ጉድጓድ በጣም ትልቅ ነው” በማለት ፍርሃቻቸውን ይገልጻሉ።
የፌዴራል መንግስት የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን በአገሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና በገለልተኛ ወገን አስጠንቶ ያገኘውና ይፋ የተደረገው ውጤት አስደንጋጭ መሆኑ ይታወሳል። በዚሁ ጥናት መሰረት ፖሊስ፣ ፍርድ ቤቶች፣ አጠቃላይ የፍትህ ተቋማትና ራሱ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ቀዳሚ ሙስና የተንሰራፋባቸው ተቋማት መሆናቸውን ማረጋገጡ፣ ተቋማቱም በጥናቱ ቅር መሰኘታቸውን በመግለጻቸው በዝርዝር ይቀርባል የተባለው ጥናት እስካሁን ይፋ ሊሆን አለመቻሉም ታውቋል፡፡
የፊታችን አርብ ቃለ መሃላ የሚፈጽሙት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ እንደ አቶ መለስ የጸረ ሙስና ኮሚሽን ተጠሪነቱ ለእርቸው ስለሆነ አዲስ በሚያቋቁሙት ካቢኔ ውስጥ መካተት የሌለባቸውን የነቀዙ ባለስልጣናት ለመለየት ፋይላቸውን ከኮሚሽኑ መውሰድ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።